ወደ የኛ ማይክሮ ፋይናንስ አ. ማ. እንኳን ደህና መጡ!
"ልናገለግልዎ ቆርጠን ተነስተናል!"
የኛ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ በፋይናንስ አገልግሎት ዘርፍ የላቀ እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በአገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማበርከት የተቋቋመ ነው፡፡ በውጤቱም ሀብት በመፍጠርና ትርፍ የሚያስገኙ የንግድ እንቅስቃሴዎችን የገንዘብ እገዛ በማድረግ ሞያዊ እና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ እንገኛለን፡፡ በቡድን በመስራት እናምናለን ፤ እንዲሁም ከደንበኞቻችን ጋር አብረን በመስራት ግባችን ላይ እንደርሳለን፡፡
አገልግሎቶቻችን
"የኛ ለሁሉም!"
የቁጠባ አገልግሎት
የገንዘብ ስርዓታችንን ለማሻሻል፣ የራሳችንን ቸግር በራሳችን ለመፍታት፣ ለምንፈልገው ጉዳይ ማዋል የምንችለውን ገንዘብ እንዲኖረን፣ በጋራ ሆነ በግል ለምንሰራው ስራ የመነሻ ካፒታል ሆኖ የሚያገለግለንና ያለንን የመወሰን አቅም የሚያዳብርልን ባለሀብት መሆን ስለምንጀምር በማህበረሰባችን ውስጥ ያለን ስፍራና ተሰሚነት ከፍ ያደርጋል፡፡
የብድር አገልግሎት
የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ብድር፣ የጥቃቅን ንግድ ብድር ፣ የፍጆታ ብድር ፣ የየግብርና ብድር፣ የቋሚ ንብረት ግዥ ብድር ፣ የመኖሪያ ቤት ብድር፣ ልዩ ብድር እና ሌሎችንም የብድር አገልግሎቶች እናቀርባለን።
የስልጠናና የማማከር አገልግሎት
የኩባንያው ሠራተኞች የብቃት ሚስጥር በየወቅቱ የሚሰጣቸው ሞያዊ ስልጠና ነው፡፡ የኛ ማይክሮ ፋይናንስ አ. ማ. ለክቡራን ደንበኞቹ ከብድርና ቁጠባ በተጨማሪ ለንግድ ሥራቸው የሚጠቅም የስልጠናና የማማከር አገልግሎት ለመስጠት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቋል፡፡
ስለ እኛ
"የኛ ለሁሉም!"
የኛ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ የተመሰረተው የላቀ የሞያ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው የፋይናንስ አገልግሎት ለሚፈልጉ ግለሰቦችና በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራየዝ ለታቀፉ ህጋዊ ማህበሮች በመስጠት ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ሀብት ለመፍጠርና ትርፍ ለማግኘት ነው፡፡
እሴቶቻችን
“የኛ ለሁሉም!”
- ጥራት ያለው አገልግሎት
- ተደራሽነትን መጨመር
- ቁርጠኝነት
- ግልጽነት
- ኃላፊነት
- ዘላቂነት
- ታማኝነት እና ጥሩ ሥነ ምግባር
የኛ - ልዩነታችን
"የኛ ለሁሉም!"
- ህብረተሰቡን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እየታገዝን በላቀ ዕውቀትና ክህሎት እናገለግላለን፡፡
- የቁጠባ ደንበኞች በሚያስቀምጡት ገንዘብ ላይ ማራኪ ወለድ ያገኛሉ፡፡
- በመካካለኛ እና በዝቅተኛ የገቢ ደረጃ ላይ የሚገኙና የተዘነጉ የሥራ ፈጣሪዎችን በብቃት እናገለግላለን፡፡
- ፈጣን ፣ ቀልጣፋና ጥሩ የደንበኞች አገልግሎት በማቅረብ መልካም ስም ያተረፉ ሠራተኞች አሉን፡፡
- በደንበኞች ፍላጎት ላይ የተመሰረተ የላቀ አገልግሎት መስጠታችን ተመራጭ ያደርገናል፡፡
- እሁድንና የምሳ ሰዓትን ጨምሮ በቀን ለ12 ሰዓት በወር ደግሞ ሰላሳውንም ቀናት የደንበኞች አገልግሎት የምንሰጥ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ነን፡፡
አጋሮቻችን
"የኛ ለሁሉም!"
- መንግሥታዊ ድርጅቶች
- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
- የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
- የኢትዮጵያ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ማህበር
- የመንግሥትና የግል ንግድ ባንኮች
- ግብረ ሰናይ ድርጅቶች
- ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች
- ማርኮን የመኪና አስመጪ
ደንበኞቻችን
የኛ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ትኩረት የሚያደርግባቸው ደንበኞች ፤ ከባንኮች አገልግሎት ማግኘት ያልቻሉትን ፣ መስራት የሚችሉ በተለይም በጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች እና ሴቶች ላይ ነው፡፡ በዋነኝነት በአዲስ አበባ እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ የሚገኙትን ደንበኞች እናገለግላለን፡፡